ፖሊስ በየሳምንቱ 20 የማስወጣት ስራ ስለሚሰራ በካሌ ሁኔታዎች እየተባባሱ ሄደዋል

ሄልቢ የተባለው ኤርትራዊ ስደተኛ እንደሚገልፀው እሱና ጓደኞቹ በረንዳ ላይ እንደሆነ ገልፆ፤ ይህም ፖሊሶች ቴንዳዎቻቸውን ሰራዎቻቸው ስለሚወስድባቸው መሆኑ ይናገራል:: የፈረንሳይ ፖሊሶች አስመልክቶ ሲናገር ፖሊሶችን ሰናይ እንሮጣለን ምክንያቱም ከዚህ በፊት ደብድበውናል ይላል::

ከኤርትራውያን ጎደኞቹ አንዱ ኢፌ የተባለው 27 ዓመት ወጣት ሲናገር ወደ እንግሊዝ አገር ለመሻገር በመሞከር ከአንድ ዓመት በላይ መቆየቱ ይገልፃል:: እሱ እንደሚለው አብዛኛዎቹ ቀናት (ለሊቶች) ፖሊሶች ስለሚያሳድዱን መተኛት አደገኛ ነው ሲል ምሬቱን ይገልፃል::

ፓውል ሌስለር  የተባለ በስደተኞች ላይ የሚሰራ ዘጋርድያን ጋዜጣ እንደገለፀው ካሌ የስደተኞች መጠልያ ያለው ሁኔታ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየባሰ መምጣቱ ይህም ጀንግል የተባለውን ዋናው የስደተኞች መጠልያ 2016 ከፈራረሰ ወዲህ መሆኑ ገልፀዋል:: አብዛኞቹ ስደተኞች 4 ሰዓታትም አይተኙም፤ ይህም የስነልቦና ጫና እንደሚያስከትልም ጭምር ይገልፃል::

የክረምቱ ጊዜም የራሱ የሆነ ተፅእኖ ይፈጥራል:: የብድር በሽታዎች እየተከሰቱ ናቸው የእንግሊዝ አገር የእርዳታ ድረጅት ተወካይ የሆነችው ማዲ አለን እንደምትገልፀው እሰካሁን ሶስት የሳምባ ነቀርሳ ታማሚዎች እንደተገኙ ትናገራለች:: በቅርቡ በየሳምንቱ ካሌ ውስጥ በሚደረገው ያማስወጣትና የማባረር ስራ ትልቅ የስነልቦና ጫና በስደተኞች ላይ እየፈጠረ መሆኑ ትገልፃለች::

አለን ጨምራ ስታስረዳም ሰዎች ሁሌም በእንቅስቃሴና መፈናቀል ላይ ናቸው አንድ ድንኳን (ቴንዳ) 6 ወራት ነበር የሚያገለግለው አሁን ግን 6 ቀናት ብቻ ነው የሚያገለግለው:: ሁኔታዎች በማይታመን ሁኔታ ከነበሩበት እጅግ በጣም የከፉ መሆናቸውም ትገልፃለች::

የፈረንሳይ ፖሊሶች በስደተኞች ላይ የሚያደርሱትን በደል በማጋለጥ ዘገባው እስካሁን 12 ወራት ውስጥ 1000 በላይ ክሶች በፖሊሶች ላይ እንደተደረጉና ከነዚህም 244 ድብደባዎችና ግርፋቶች እንደሁም አስለቃሽ ጋዝ መጠቀማቸውም ይገለፃል::

በካሌ ያለው ሁኔታ ስደተኞችን በጀልባ ወደ ኢንግሊዝ አገር እንዲሻገሩ እየገፋፋቸው መሆኑና ቴሌግራፍ በቅርቡ እንደዘገበው 28 ጀልባዎች ወደ ኢንግሊዝ ሲሻገሩ በፈረንሳይ ባለስልጣናት መያዛቸው ገልፀዋል::

TMP – 7/12/2018

ፎቶ:- ኤድዋርድ ክሮፎርድ/ ሻተርስቶክ። የፈረንሳይ ፖሊሶች ከካሌ የስደተኞች ማእከል ሲወጡ